የእስልምና ሃይማኖት

ቁርኣን እና ከሰዎች ሁሉ ምርጥ የሆኑት ነብይ ሓዲሦች እንደገለፁት

መ – ነቢዩ ሁድ (የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን)

ከዚያም ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አላህ አሕቃፍ በምትባል አካባቢ ወደሚኖሩ ዓድ ነገድ ማህበረሰብ ‐ጠምመው ከአላህ ውጭ ማምለክ በጀመሩ ጊዜ – ከእነሱ የሆኑትን ሁድ (የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን) መልእክተኛ አድርጎ ላከላቸው።

ይህንንም በማስመልከት የላቀው አላህ በሚከተለው መልኩ ነግሮናል፦

{ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን። «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ። ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም። (የአላህን ቅጣት) አትፈሩምን» አላቸው።}

{ከሕዝቦቹ እነዚያ የካዱት መሪዎች «እኛ በሞኝነት ላይ ኾነህ በእርግጥ እናይሃለን። እኛም ከውሸተኞቹ ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን» አሉት።}

{(እርሱም) አላቸው «ወገኖቼ ሆይ! እኔ ሞኝነት የለብኝም። ግን እኔ ከዓለማት ጌታ የተላክሁ ነኝ።»}

{«የጌታዬን መልክቶች አደርስላችኋለሁ። እኔም ለእናንተ ታማኝ መካሪ ነኝ።»}

{«ከጌታችሁ የኾነ ግሣጼ ከእናንተው ውስጥ ባንድ ሰው ላይ ያስጠነቀቃችሁ ዘንድ ቢመጣባችሁ ትደነቃላችሁን ከኑሕም ሕዝቦች በኋላ ምትኮች ባደረጋችሁና በፍጠረትም ግዙፍነትን በጨመረላችሁ ጊዜ አስታውሱ። የሻችሁትንም ታገኙ ዘንድ የአላህን ጸጋዎች አስታውሱ።»}

{«አላህን ብቻውን እንድንገዛ አባቶቻችንም ይገዙት የነበረውን (አማልክት) እንድንተው መጣህብን ከውነተኞች ከኾንክ የምታስፈራብንን (ቅጣት) አምጣብን» አሉ።}

{«ከጌታችሁ የኾነ ቅጣትና ቁጣ በእናንተ ላይ በእውነት ተረጋገጠ። እናንተና አባቶቻችሁም (አማልክት ብላችሁ) በጠራችኋቸው ስሞች አላህ በእርሷ ምንም ማስረጃ ያላወረደባት ስትኾን ትከራከሩኛላችሁን ተጠባባቁም እኔ ከእናንተ ጋር ከተጠባባቂዎቹ ነኝና» አለ።}

{እርሱንና እነዚያንም አብረውት የነበሩትን ከእኛ በኾነው ችሮታ (ከቅጣት) አዳንናቸው። የእነዚያንም በተአምራታችን ያስተባበሉትንና አማኞች ያልነበሩትን መሠረት ቆረጥን።}

[አል-አዕራፍ፡ 65-72]

አላህም በእነሱ ላይ ለስምንት ቀናት ውስጥ በጌታዋም ፍቃድ ሁሉንም ነገር በምታጠፋ በሆነች የምትንሿሿ ብርቱ ነፋስን ላከባቸው፤ ነብዩሏህ ሁድ(የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን) እና እነዚያን ከእርሳቸው ጋር ያመኑትን አላህ አዳናቸው።

About The Author